“እግዚአብሔር ‘ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች’ ነው እንጂ ያለው ወደ አሜሪካና ኃያላን አገራት ትዘረጋለች አላለም” - ሻሎም ተስፋዬ

Ethiopian community

Helen Michael (L), Michael Feleke (C), Eyob Esubalew (T-R) and Shalom Tesfaye (B-R) Source: Supplied

የአውስትራሊያ ነዋሪ ኢትዮጵያውያን ኢዮብ እሱባለው (ሜልበርን - ቪክቶሪያ)፣ ሻሎም ተስፋዬ (አደላይድ - ምዕራብ አውስትራሊያ)፣ ሚካኤል ፈለቀ (ፐርዝ - ምዕራብ አውስትራሊያ) እና ሄለን ሚካኤል (ሜልበርን - ቪክቶሪያ) ሰሞኑን የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ ያመላከቱትን ‘የአስተዳደራቸውን’ አቋም ተፃርረው አተያዮቻቸውን ገልጠዋል።


አንኳሮች


 

  • አንድነታችንን ካጠናከርን ማንንም መመከት እንችላለን፤ የግድቡ የኔ ስሜታችንን በቦንድ ግዢና ስጦታ እንግለጥ - ኢዮብ እሱባለው
  • በፕሬዚደንቱ ተራ ንግግር መሸበር የለብንም፤ ኢትዮጵያ አገራችንን ማንም እንዲነካብን ማንቀላፋት የለብንም። አገራችንን እንጠብቅ - ሄለን ሚካኤል
  • እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ሊጎበኝ የተነሳበት ሰዓትና ወቅት ስለሆነ ‘ትራምፕ ምን ይላል?’ ሳይሆን፤ ‘እግዚአብሔር ስለ ኢትዮጵያ ምን ይላል?’ የሚለውን ማሰቡና ማስተዋሉ ላይ ትኩረት ማድረጉ መልካም ነው ብዬ አስባለሁ - ሻሎም ተስፋዬ
  • ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን ከተሰለፍን የወደፊት ዕጣ ፈንታችንን ማረጋገጥ እንችላለን፤ በውስጥ ችግራችን ክፍተት ከተፈጠረ ያለው ጉስቁልና፣ ድህነትና ድንቁርና ሊቀጥል ይችላል - ሚካኤል ፈለቀ

Share